የኡስታዙ ውዝግብ
የእግዚአብሄር ፍጥረት የመጀመሪያው ማነው? ጉማሬ? ሰማይናምድር? ወይስ ኢየሱስ? ብሎ ድንክርክር ላለው ኡስታዝ ወሒድ የተሰጠ መልስ! ይህ ሰው እራሱን የግሪክ እና የእብራይስጥ አስተማሪ አድርጎ የሾመ ሰው ሲሆን ይህን ተገን አድርጎ ሙግቶችን በእነዚህ ቋንቋዎች የሚያቀርብ ሰው ነው። ለጠየቀውን ጥያቄ ከዚህ በታች የእርሱንም እውቀት እየገመገምን እንመልከተው፦ ጥያቄውም፦ የእግዚአብሄር ፍጥረት የመጀመሪያው ማነው? ጉማሬ? ሰማይናምድር? ወይስ ኢየሱስ? በመጀመሪያ ይህን ጥያቄ ለምን እንደተነሳ ከታች የምናየው ቢሆንም ጥያቄው የተነሳው መፅሀፍ ቅዱስን ጠንቅቆ ካለመረዳትና ከድርቅና የሆነ እንጅ እግዚአብሄር በመጀመሪያ ሰማይንና ምድርን እንደፈጠረ በዘፍጥረት 1:1 ላይ በግልፅ " እግዚአብሔር መጀመሪያ ሰማይንና ምድርን ፈጠረ " ተብሎ የተነገረ ሲሆን ጠያቂው ግን ይህን እንዳላዩ አልፎ በእሱ ሀሳብ መጀመሪያ ተፈጠሩ የሚላቸውን የመፅሀፍ ቅዱስን ቃል በማጣመም አስቀምጧል። በመቀጠልም... A-ጉማሬ፦ ከአንተ ጋር የሠራሁትን ጉማሬ፥ እስኪ፥ ተመልከት፤ መጽሐፈ ኢዮብ 40 : 15 እርሱ የእግዚአብሔር ፍጥረት አውራ ነው፤ መጽሐፈ ኢዮብ 40 : 19 He [is] the chief of the ways of God: he that made him can make his sword to approach [unto him]. Job 40 : 19 አውራ ተብሎ የተቀመጠው ቃል መጀመሪያ the first የዕብራይስጡ ደግሞ "ረሺት" ማለት ሲሆን ለሰማይና ምድር መጀመሪያነት ተጠቅሷል።] መልሴ፦ በመጀመሪያ "רֵאשִׁ֤ית"(reshit) የምትለው ቃል የፍጥረትን መጀመሪያ ለመጥቀስ ብቻ የምትውል ናት የሚል ድምዳሜ በዕብራይስጥ የቋንቋ ህግ የለም አይኖርምም። እ